ቀርሜሎስ እንገናኝ [1/2]

ታላቁ ነቢይ ኤልያስ በዘመኑ የእግዚአብሄርን ህዝብ ካሳተው አጋንንታዊ አሰራር ጋር ሲዋጋ የኖረ፣ ህዝቡን ወደ አምላኩ ሊመልስ የታገለ እንዲሁም በፍጻሜው ወዳገለገለው አምላክ በክብር የተሰበሰበ የእምነት ሰው ነበር፡፡ነቢዩ በዘመኑ በእስራኤል ምድር ላይ በነገሰው የባእድ አማልክት ምክኒያት በህዝቡ ላይ የመጣውን የእግዚአብሄር ተግሳጽ ለንጉሱ አመልክቶታል፡- ”በገለዓድ ቴስቢ የነበረው ቴስብያዊው ኤልያስ አክዓብን፡- በፊቱ የቆምሁት የእስራኤል አምላክ ሕያው እግዚአብሔርን! ከአፌ ቃል …
Continue reading ቀርሜሎስ እንገናኝ [1/2]

መመለሰ – ለእውነት ንሰሀ

መታረቅ፣ መስማማት፣ ሰላም ማውረድ፣ መቀራረብና የመሳሰሉት የሰላም ማስቀጠያ መንገዶች በማህበረሰብ ውስጥ ትልቅ ስፍራ አላቸው፡፡ የሰው ልጅ የአብሮነት እሴትን በልቡ አትሞ ስለያዘ በተለይ እርቅ በሚባል የአንድነት ማሰሪያ ላይ ትልቅ አትኩሮት አለው ሊባል ይቻላል፡፡ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ መታረቅን ይሻና መታረቂያውን የማይስማማበት አጋጣሚ ይገጥመዋል፡፡ሁላችን ብንሆን እርቅ ሰላም እንደሆነ ይገባናል ስለዚህ እንስማማበታለን፡፡የእርቁን ሂደት ወይም አላማ ግን ልንወድደው ካልቻልን አንቀበለውም፡፡ለምሳሌ …
Continue reading መመለሰ – ለእውነት ንሰሀ

ያለመታዘዝ ጠንቅ

ታዝዘው የቀረቡና የተጠጉ ልባቸው ከእምነት በዛለ ጊዜ ያለመታዘዝ እንደሚያሸንፋቸው ቃሉ ያስተምራል፡፡ታዝዘው ወደ ምድረ-በዳ የወጡት እስራኤላውያን ባልታዘዙ ወቅት በነበሩበት ምድረ-በዳ አልቀዋል፡፡ድምጹን እየሰሙ ለድምጹ ተግባራዊ ምላሽ የማይሰጡ በህይወት ላይ በሚፈጠር ጠንቅ ይጠቃሉ፡፡እግዚአብሄር በባሪያው በኢያሱ እጅ ምሪትን ብቻ ሳይሆን እረፍትን ሊሰጣቸው እቅድ ነበረው፡፡እስራኤላውያን ግን ባለመታዘዛቸው የታሰበላቸውን ሊያገኙ አልቻሉም፡፡ ዕብ.4:6-9 ”እንግዲህ አንዳንዶች በዚያ እንዲገቡ ስለ ቀሩ፥ ቀድሞም የምስራች የተሰበከላቸው …
Continue reading ያለመታዘዝ ጠንቅ

መንፈሳዊ ሪቫይቫል- ከሴኬም ወደ ቤቴል ተመለስ!

እግዚአብሄር ያእቆብን ስለወደደው ወደ በረከቱ ስፍራ እንዲመለስ አስታወሰው፡- ዘፍ.35:1-10 እግዚአብሔርም ያዕቆብን አለው፡- ተነሥተህ ወደ ቤቴል ውጣ፥ በዚያም ኑር፤ ከወንድምህ ከዔሳው ፊት በሸሸህ ጊዜ ለተገለጠልህ ለእግዚአብሔርም መሠውያውን አድርግ።ያዕቆብም ለቤተ ሰቡና ከእርሱ ጋር ላሉት ሁሉ እንዲህ አለ። እንግዶቹን አማልክት ከመካከላችሁ አስወግዱ፥ ንጹሐንም ሁኑ፥ ልብሳችሁንም ለውጡ፤ ተነሥተንም ወደ ቤቴል እንውጣ፤ በዚያም በመከራዬ ጊዜ ለሰማኝ፥ በሄድሁበትም መንገድ ከእኔ ጋር …
Continue reading መንፈሳዊ ሪቫይቫል- ከሴኬም ወደ ቤቴል ተመለስ!

አሮጌው ወይስ አዲሱ ሰው?[2/2]

ሰው ህያው የሆነ ነፍስና የሚረግፍ ስጋ ውህደት ነው።ህያው ነፍስ ከእግዚአብሄር እፍ ከተባለ የህይወት እስትንፋስ ስለተገኘች የምትጠፋ አይደለችም፣ ረቂቅና መንፈሳዊ ስለሆነች የመታየትም የመዳሰስም ችሎታ የላትም።ስጋ ግን የአፈር(ምድራዊ) ነው፣ ግኡዝ፣ የሚታይና የሚዳሰስ ጭምር። ዘፍ.2:7 ይህን ያረጋግጥልናል፦ “እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት፤ ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ።“ እውነታው እንደሚያሳየን የምድር አፈር ደቃቅ፣ …
Continue reading አሮጌው ወይስ አዲሱ ሰው?[2/2]

በዘመን መሀከል እግዚአብሄር

የባቢሎን ምድር በገነነችበት ዘመን ምድሪቱን ያሳወቁትና ዝናዋን ከፍ ያደርጉት ነገስታቶችዋ ብቻ አልነበሩም፡፡ምድሪቱዋ የመናፍስት መናሀሪያ እንደመሆንዋ በአማልክቶቹዋ ብዛትም የታወቀች ነበረች፡፡የመንግስታቶችዋ ዝና፣ ስመጥር ስራዎችና ወረራዎች እንዲሁም ጠቢባኖችዋ በዘመኑ ከፍ ያሉ ነበሩ፡፡በነዚያ ዘመናት መካከል ግን የእስራኤል አምላክና የባቢሎን አማልክት የሚወዳደሩበት አውድና አጋጣሚ ተፈጠረ፡፡በአጋጣሚው መሀል ህያው አምላክ የመረጣቸው ህዝቦች ከአህዛብ መሃል ተገኙ፤ የአይሁድ በባቢሎን መገኘት ግን የእንግድነት ሳይሆን ይምርኮና …
Continue reading በዘመን መሀከል እግዚአብሄር

ዲያቢሎስን መቃወም

ክርስቲያኖች ጠላትን ስንቃወም በቃልም በስራም እንቃወመዋለን።የመቃወሚያ መሳሪያችን ደግሞ በመንፈስ የምንጠራው የኢየሱስ ስም ነው። ጠላትን ለመቃወም ስንነሳ ለምን እርሱን እንደምንቃወመውና ተቃውሞአችን ምን እንደሚሰራ/ውጤቱ ምን እንደሆነ ማወቅ ያስፈልጋል።በቅድሚያ ለመቃወም ምክኒያታችን ዲያቢሎስ የሚያቅዳቸውና የሚሰራቸው የክፋት ስራዎቹ ናቸው። በተጨማሪ በክፉ ባህሪው ምክኒያትም እንቃወመዋለን። የህይወታችን ጥፋት መሰረቱ እሱ ነው፣የምንኖርበትን ማህበረሰብና የኑሮ ሲስተምም የተቆጣጠረው እሱ ነው። ለመቃወም መቃወሚያ መንገዱን መረዳት ይጠይቃል። …
Continue reading ዲያቢሎስን መቃወም

የቸርነቱን ደውል አስተውል

የእግዚአብሄርን ባህሪ የሚገልጥ አዋጅ እንዲህ ይላል፡- ዘጸ.34:6-8 ”… እግዚአብሔር፥ እግዚአብሔር መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት፥እስከ ሺህ ትውልድም ቸርነትን የሚጠብቅ፥ አበሳንና መተላለፍን ኃጢአትንም ይቅር የሚል፥ በደለኛውንም ከቶ የማያነጻ፥ የአባቶችንም ኃጢአት በልጆች እስከ ሦስትና እስከ አራት ትውልድም በልጅ ልጆች የሚያመጣ አምላክ ነው ሲል አወጀ።ሙሴም ፈጥኖ ወደ መሬት ተጐነበሰና ሰገደ።” የእግዚአብሄርን ምህረትና ቸርነት የሚያውቁ ቅዱሳን …
Continue reading የቸርነቱን ደውል አስተውል

የታላቁ ጠላት ጥቂቱ

ብዙ ጊዜ ጥቂት ያልነው አነስተኛ ወይም አይን የማይገባና ጉልበቱን ቸል ያልነው ኢምንት ነገር ብዙሀኑን ሰርስሮ በመግባት በክሎና ተሰራጭቶ በራሱ ባህሪ ሲውጠው እናያለን፡፡የእግዚአብሄር ቃል ጥቂት እርሾ ሙሉውን ሊጥ እንደሚያቦካ ያስረዳል፡፡ጥቂት እርሾ ውስጥ ያለ ኮምጣጣ ነገር የመሰራጨት ጉልበቱ ከፍተኛ በመሆኑ ንጹሁንና ትኩሱን (ያልከረመውን) ሊጥ በፍጥነት ያቦካዋል/ያኮመጥጠዋል፡፡ነገሩ በእኛም ህይወት ውስጥ ሲመጣ እንዲሁ ነው፡፡እንደ እርሾው የኮመጠጠና የማይመች ነገር ከእኛ …
Continue reading የታላቁ ጠላት ጥቂቱ

በእምነት መመላለስ

በእስራኤል ነገድ ውስጥ የእግዚአብሄርን ህግ ሊጠብቅ የቻለ ሰው አልነበረምና እግዚአብሄር በዚያ ባለመደሰቱ የተናገረው ቃል ይህ ነው፦ “የእግዚአብሔርን ኪዳን አልጠበቁም፥ በሕጉም ለመመላለስ እንቢ አሉ“ (መዝ.78:10) ያኔ የእግዚአብሄር የግርዘት ቃል ኪዳን በእስራኤል የምድረበዳ ጉዞ ወቅት ተዘንግቶ ነበር።በሌላ መልኩ እስራኤላውያን ከነአን ከገቡ በሁዋላም በሲና ተራራ ፊት ሆነው የተቀበሉትን ህግ እንዲሁ አልጠበቁም።ዛሬም ቢሆን እየሆነ ያለው ተመሳሳይ ነው፡፡ እኛስ ራሳችን …
Continue reading በእምነት መመላለስ