የታላቁ አምላክ ሀይል(3..)

ወንጌል በሀይል የሚሰበክ የምስራች ቃል ነው፡፡ ወንጌል በውስጡ ሀይል አለበት፣ የእግዚአብሄር ፈቃድ በውስጡ ስላለና እግዚአብሄር የሚሰራበት የመስቀሉ ቃል መገለጫ በመሆኑ፡፡ ወንጌል የጌታን የደህንነት ስራ የሚገልጥ አዋጅ ነው፤ ስለሆነም እግዚአብሄር አለም ሳይፈጠር ቅዱስ ሊሆኑ በተጠሩ ህይወቶች ውስጥ ሊፈጥር ያቀደውን ጽድቅ በክርስቶስ ኢየሱስ መከራ፣ ሞትና ትንሳኤ በኩል እንደፈጸመው ከፍ አድርጎ የሚያውጅ ቃል ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስ ለሰዎች ሊሰጥ …
Continue reading የታላቁ አምላክ ሀይል(3..)

ወድጃችኋለሁ ይላል እግዚአብሔር

ወድጃችሁዋለሁ የሚል የአምላክ ድምጽ እንዴት ያለ እረፍት፣ እንዴት ያለ ደስታ፣ እንዴት ያለ ሰላም የሚፈጥር መተማመኛ ቃል ነው? እንኩዋን የአምላክ ድምጽ የምንደገፈው ሰው እንኩዋን ይህን ቃል ቢያሰማን ልባችንን ያሞቀዋል፡፡ እግዚአብሄር የጠራውን ህዝብ ሊያጸናና በጉዞው መሀል ሊያበረታው እንዲህ ያለ ቃሉን ይልካል፡፡ አብራምን ስንመለከት እርሱ ተስፋ ቆርጦ ሳለ ቃሉ በዘፍ.15:1-6 ሲመጣለት እናያለን፡- ”ከዚህ ነገር በኋላም የእግዚአብሔር ቃል በራእይ …
Continue reading ወድጃችኋለሁ ይላል እግዚአብሔር

እግዚአብሄር የተናገረውን በጊዜው ይፈጽማል‹2..›

እግዚአብሄር የተናገረውን እንደተናገረው ልክ/ ፍጹም አድርጎ በትውልድ መሃል በጊዜው እንዲገልጠው የተመቻቸ ስፍራ/ማረፍያ ልብ ይፈልጋል፡፡ በአዲስ ኪዳን ሊሆን የተጠበቀው፣ የሆነውም ይህ ነበር፤ ስለዚህ የእግዚአብሄር መልአክ የእግዚአብሄርን ስራ ሊያውጅ ሲገለጥ ወደ ሁለት ቤተሰቦች ዘንድ ሄደ፡- ወደ ካህኑ ዘካርያስና ወደ ማርያም ቤት፡፡ ዘካርያስና ሚስቱ እልሳቤጥ በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ። ማርያም ለዮሴፍ …
Continue reading እግዚአብሄር የተናገረውን በጊዜው ይፈጽማል‹2..›

የውሳኔና ስምምነት አግባብ‹1…›

ወሳኝነት አባት የሆነው እግዚአብሄር ለፈጠራቸው የሰው ልጆች ያስተማረው ስልጣን ነው፡፡ ውሳኔ ከትእዛዝ ሰጪ አካል ይወጣል፣ ስልጣን በውሳኔ ተግባራዊነት ይገለጣል፣ እንዲሁም የእግዚአብሄር ውሳኔ ፍጹምና ሊታዘዙት የተገባ ሲሆን የእኛ ግን የሚዋዥቅና አቅም የሌለው ነው (በተለያዩ ምክኒያት ሰው ውሳኔውን ይለዋውጣል)፡፡ ለምሳሌ በዘጸ.9:5-7 ውስጥ ስለእግዚአብሄር ወሳኝነት ሲናገር፡- ”እግዚአብሔርም፡- ነገ እግዚአብሔር ይህን ነገር በምድር ላይ ያደርጋል ብሎ ጊዜን ወሰነ። እግዚአብሔርም …
Continue reading የውሳኔና ስምምነት አግባብ‹1…›

የታላቁ አምላክ ሀይል(2..)

እግዚአብሄርንና ሀይሉን የሚያውቁ ሰዎች በሁኔታዎች አካሄድና በነገሮች መፈጠር አይደናገጡም፣ በአጋጣሚዎች ድንገት መከሰት አይርበተበቱም፤ ምክኒያቱም ከእነርሱ በላይ ያለውን ስለሚያወቁ፣ ከርሱ በቀር ማንም እንደሌለ ስለሚረዱ፣ ያለ እርሱ ፈቃድ የሚሆን ነገር እንደሌለ ስለሚያውቁ፣ ደግሞም የእርሱ አሳብ ለሰው ልጆች ሁሉ መልካም መሆኑን ስለሚያስተውሉ ነው፡፡ ነቢዩ ኤልሳ በአስጨናቂ ጠላቶች ተከቦ ሳለ የተናገረውን እንመልከት፡- 2ነገ.6:15-17 ”የእግዚአብሔር ሰው ሎሌ ማለዳ ተነሥቶ በወጣ …
Continue reading የታላቁ አምላክ ሀይል(2..)

ስለ መስቀሉ ቃል ‹2..›

የመስቀሉ ቃል የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን መከራ መቀበልና በሀይል ከሞት መነሳት የሚሰብክ የወንጌል ክፍል ነው፡፡ በዕብ.9:28 እንደተጻፈው፡- ”እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ፥ የብዙዎችን ኃጢአት ሊሸከም አንድ ጊዜ ከተሰዋ በኋላ፥ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁት ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል።” ይላል፡፡ የሚበላ የህይወት እንጀራ ክርስቶስ ህያው በሆነው ስጋውና ደሙ ሊቀድሰንና ህይወትን ሊሰጠን ተገልጦአል፡፡ ወንጌልን አስደሳች የሚያደርገው በእርሱ መከራ የእኛ ደህንነት በመረጋገጡ፣ …
Continue reading ስለ መስቀሉ ቃል ‹2..›

የታላቁ አምላክ ሀይል(1..)

የእግዚአብሄር ሀይል ወይም መለኮታዊ ሀይል ከእግዚአብሄር ባህሪያት መሀል አንደኛው ነው፡፡ እግዚአብሄር አምላክ ነው፣ ጌታ ነው፣ መድሀኒት ነው፣ ሁሉን የሚችል፣ ሁሉን የሚገዛ፣ በሁሉ የሚኖር፣ ሁሉን በራሱ፣ ለራሱና ከራሱ ያደረገ ድንቅ አምላክ ነው፡፡ ይህ አምላክ ሁሉን በሀይሉ ያደርጋል፡፡ ሀይሉ ጉልበቱን የማንቀሳቀሻ ብርታቱ ነው፡፡ ዘዳ.10:16፤17”እንግዲህ አምላካችሁ እግዚአብሔር የአማልክት አምላክ የጌቶችም ጌታ፥ ታላቅ አምላክ ኃያልም የሚያስፈራም፥ በፍርድ የማያደላ፥ መማለጃም …
Continue reading የታላቁ አምላክ ሀይል(1..)

ስለ መስቀሉ ቃል ‹1..›

የእግዚአብሄር ቃል ስለ መስቀሉ ቃል በ1ቆሮ.1:18 ላይ እንዲህ ይላል፡- ”የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።” በመስቀሉ ቃል እውቀት ላይ የሚቀርቡ አሳቦች ወይም የሚንጸባረቁ አቁዋሞች የአማኝን የእምነት ይዘት ይወስናሉ፣ ያም ብቻ አይደለም የዘላለም አድራሻውን ጭምር ይወስናሉ፡፡ ለሚያምኑት ቃሉ የእግዚአብሔር ኃይል ሲሆን ለማያምኑት ሞኝነት (ከንቱና የማይረባ አሳብ ብቻ) ይሆንባቸዋል፡፡ ሰዎች ከንቱና የማይረባ ብለው …
Continue reading ስለ መስቀሉ ቃል ‹1..›

የጠላትን መንገድ እወቅ[3…]

የነህሚያ ተግዳሮት ነህሚያ ለእግዚአብሄር ህዝብና ለመቅደሱ የቀና አገልጋይ ነበር፡፡ የኢየሩሳሌም ፈርሳ መቅረትና የመቅደሱ ስርአት መቆም እያስጨንቀው በባእድ አገር ለብዙ ዘመናት ኖሮአል፡፡ በእግዚአብሄር ሰአት ከሚኖርበት የምርኮ ምድር ተነስቶ ወደ ገዛ ምድሩና ህዝቡ በመጉዋዝ አገሩ ደረሰና ቀጥታ ወደ ስራ ገባ፡፡ የነህሚያ ተግዳሮት የሚጀምረው ገና እግሩ ኢየሩሳሌምን ከረገጠ ጊዜ አንስቶ ነበር፡፡ ጠላቶች በእግዚአብሄር አምልኮና ስርአት ስለማይደሰቱ የከተማይቱና የመቅዱስ …
Continue reading የጠላትን መንገድ እወቅ[3…]

እግዚአብሄር የተናገረውን በጊዜ ይፈጽማል‹1..›

እግዚአብሄር ሲናገር፡-”ቃሌ ከአፌ በጽድቅ ወጥታለች፥ አትመለስም” ይላል (ኢሳ.45:23)፡፡ እግዚአብሄር ይናገር እንጂ የተናገረው መሆኑ/መፈጸሙ አይቀርም፡፡ ስልጣን ያለው ቃል አሳቡን ማከናወን እንደማይሳነው እንኩዋን ህያው አምላክ ከሰው የሆነ ባለስልጣንም በችሎታው አይጠረጠርም፡፡ የእግዚአብሄር ንግግር ለመከናወኑ እርግጠኛ/እውነት በመሆኑ ሲናገር የሰሙት ሰዎች የተናገረውን ቃል በደስታና በተስፋ ይዘው ይጠባበቁታል፡፡ መጠበቅ እንዲህ እንደምንለው ቀላል አይደለም፡- ትግስት ይጠይቃል፣ እምነት ይጠይቃል፣ ጊዜም ይጠይቃል፡፡ ቢሆንም የታመኑት …
Continue reading እግዚአብሄር የተናገረውን በጊዜ ይፈጽማል‹1..›