ነጻ የወጣ ህዝብ[1…]

የባርነት ሸክሞች ነበሩ… እነዚህ ሰውን የሚያጎብጡ፣ የሚያስሩ፣ የሚያስጭንቁ፣ የሚያውኩ ነበሩ። የተሸከማቸውን አያነቃንቁ፣ አያራምዱ፣ አያዘረጉ እረፍትም አይሰጡ። ጌታ ኢየሱስ ግን ከእኛ ላይ አወረዳቸው። ከሸክም በሁዋላ ጎብጦ መቅረትም አለ፣ የእስራት ጠባሳ ፈሪ አድርጎም ያስቀራል፣ የሚያስጨንቁም ለቀው ቢሄዱም በሩቅ ቢያስፈራሩ ዋስትናችን ጌታ ኢየሱስ ካለን ብቻ መፍትሄ ይሰጣል፤ እምነት በእርሱ ላይ ባለን መደገፍ፣ እርሱን በህይወታችን በማንገስ፣ ይሄ ልምምድ ብቻ …
Continue reading ነጻ የወጣ ህዝብ[1…]

የመሰረቱ ማጠንጠኛ (2…)

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ በመንፈሳዊ ህይወታችን መቆምያ፣ መጽኛችንና እምነታችንን በድል ማጠናቅቅ የሚያስችል የስኬታችን መሰረት ነው። እርሱ ሲናገር ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም ብሎአል። ጌታ ኢየሱስ ለእኛ የሁሉ ነገራችን መሰረት ነው፦ ”እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ስለዚህ እናንተ አስቀድሞ በሥጋ አሕዛብ የነበራችሁ፥ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ …
Continue reading የመሰረቱ ማጠንጠኛ (2…)

የመሰረቱ ማጠንጠኛ (1…)

መሰረት ማለት? መሰረት መነሻ ነው፣ መሰረት መቆሚያ ነው፣ መሰረት የእድገት መጀመሪያ ነው፣ መሰረት ስር ነው፣ መሰረት መስፋፊያ ነው፣ መሰረት መታመኛ ነው፣ መሰረት አቁዋም ነው፣ መሰረት መታወቂያ ነው፣ መሰረት ምንጭም ነው። እያንዳንዱ ነገር መሰረት ያለውና በዚያ ላይ የቆመ፣ የታነጸና ያደገ ነው። ለምሳሌ የምድር መሰረት በእግዚአብሄር ስለተመሰረተ የማይናወጥ ሆኖ ይኖራል። እንዲያውም መሰረቷ ቢናወጥ የሚያናውጣት ሌላ ሃይል ሳይሆን …
Continue reading የመሰረቱ ማጠንጠኛ (1…)

የውሳኔና ስምምነት አግባብ (3…)

ወስኖና ተስማምቶ መኖር ንጉስ ዳዊት ስለ እግዚአብሄር ማንነት ጠንቅቆ የሚያውቅ ሰው ስነለነበር ከእርሱ ጋር ተስማምቶ ለመኖር (ሲሳሳት እንኩዋን ፈጥኖ በይቅርታ ለመስማማት) የማያቅማማ ሰው ነበር፡፡ ይህ ፍላጎቱም የተሳካለት ሰው ነበር፡፡ በመዝ.130:3-8 ውስጥ ሲናገር፡- ”አቤቱ፥ ኃጢአትንስ ብትጠባበቅ፥ አቤቱ፥ ማን ይቆማል? ይቅርታ ከአንተ ዘንድ ነውና። አቤቱ፥ ስለ ስምህ ተስፋ አደረግሁህ፤ ነፍሴ በሕግህ ታገሠች። ከማለዳው ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊት …
Continue reading የውሳኔና ስምምነት አግባብ (3…)

አዲስ ኪዳን ምልክት  (2..)

​​​​​​​​የአዲስ ኪዳን ምልክት ሰው በብሉይ ኪዳን የነበረ አንድ ነቢይ በህይወቱ የተከናወነ አዲስ ልምምድ ማስተናገዱ ከግርምት ባለፈ ለትውልዱ የሚያበስረው ትልቅ ምልእክት ነበረው፡፡ ​​​​ነቢዩ ዮናስ  ይባላል፣ ይህ ነቢይ በአንድ ወቅት ከእግዚአብሄር ፊት የሚኮበልልበት ሰበብና ጥሪውን ወደ ሁዋላ የሚያደርግ ድካም ገጥሞት ነበር፤ እግዚአብሄር ግን መኮብለሉን አይቶ ሳይተወው በመከታተል እስከተደበቀበት ስፍራ እስከ ጥልቅ ድረስ ወርዶ የሚያስተምረውን እርምጃ ሲወስድበት ይታያል፡፡ …
Continue reading አዲስ ኪዳን ምልክት  (2..)

የመለያችን ምልክት (1..)

እግዚአብሄር ምልክት የሚያኖርባቸው ሰዎች በእግዚአብሄር የታዩ ሰዎች ናቸው፤ በእርሱ ከለላ ውስጥ ያሉ በአላማው ውስጥ የተቀመጡም ናቸው፡፡ በእግዚአብሄር እቅድ ላይ በክፋት የተነሳው ቃየን እንኩዋን ከሚያገኘው ክፋት ይጠበቅ ዘንድ በሰዎች ዘንድ የመጀመሪያ የሆነውን ምልክት ከእግዚአብሄር ተቀብሎአል፡፡ ይህ ምልክት እርሱን በሰራው ሀጢያት ከመጥፋት የሚታደገው የእግዚአብሄር ምልክት ነበር፡፡ እግዚአብሄር ለራሱ ለለየው ህዝብ ደግሞ የተለየ ጥበቃ በማድረግ ምልክት በላዩ ላይ …
Continue reading የመለያችን ምልክት (1..)

የውሳኔና ስምምነት አግባብ ‹2…›

ከእግዚአብሄር ጋር መስማማት ቃሉ ተስማምተን ከእግዚአብሄር ጋር ስንኖር የሚሆነውን ሁኔታ ሲያስረዳ እንዲህ ይላል፡- ”የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ብትጠብቅ፥ በመንገዱም ብትሄድ፥ እግዚአብሔር እንደ ማለልህ ለእርሱ የተቀደሰ ሕዝብ አድርጎ ያቆምሃል። የምድር አሕዛብም ሁሉ የእግዚአብሔር ስም በአንተ ላይ እንደ ተጠራ አይተው ይፈሩሃል። እግዚአብሔርም እርስዋን ይሰጥህ ዘንድ ለአባቶችህ በማለላቸው በምድርህ ላይ፥ በሆድህ ፍሬ፥ በከብትህ ፍሬ፥ በእርሻህም ፍሬ፥ እግዚአብሔር በጎነቱን በላይህ …
Continue reading የውሳኔና ስምምነት አግባብ ‹2…›

የውሳኔና ስምምነት አግባብ‹1…›

ወሳኝነት አባት የሆነው እግዚአብሄር ለፈጠራቸው የሰው ልጆች ያስተማረው ስልጣን ነው፡፡ ውሳኔ ከትእዛዝ ሰጪ አካል ይወጣል፣ ስልጣን በውሳኔ ተግባራዊነት ይገለጣል፣ እንዲሁም የእግዚአብሄር ውሳኔ ፍጹምና ሊታዘዙት የተገባ ሲሆን የእኛ ግን የሚዋዥቅና አቅም የሌለው ነው (በተለያዩ ምክኒያት ሰው ውሳኔውን ይለዋውጣል)፡፡ ለምሳሌ በዘጸ.9:5-7 ውስጥ ስለእግዚአብሄር ወሳኝነት ሲናገር፡- ”እግዚአብሔርም፡- ነገ እግዚአብሔር ይህን ነገር በምድር ላይ ያደርጋል ብሎ ጊዜን ወሰነ። እግዚአብሔርም …
Continue reading የውሳኔና ስምምነት አግባብ‹1…›

የጠላትን መንገድ እወቅ[3…]

የነህሚያ ተግዳሮት ነህሚያ ለእግዚአብሄር ህዝብና ለመቅደሱ የቀና አገልጋይ ነበር፡፡ የኢየሩሳሌም ፈርሳ መቅረትና የመቅደሱ ስርአት መቆም እያስጨንቀው በባእድ አገር ለብዙ ዘመናት ኖሮአል፡፡ በእግዚአብሄር ሰአት ከሚኖርበት የምርኮ ምድር ተነስቶ ወደ ገዛ ምድሩና ህዝቡ በመጉዋዝ አገሩ ደረሰና ቀጥታ ወደ ስራ ገባ፡፡ የነህሚያ ተግዳሮት የሚጀምረው ገና እግሩ ኢየሩሳሌምን ከረገጠ ጊዜ አንስቶ ነበር፡፡ ጠላቶች በእግዚአብሄር አምልኮና ስርአት ስለማይደሰቱ የከተማይቱና የመቅዱስ …
Continue reading የጠላትን መንገድ እወቅ[3…]

እንደተከፈለልህ ተመላለስ (2..)

እንደተከፈለልን ለመመላለስ ከወሰንን እግረመንገዳችንን ከእግዚአብሄር የተቀበልነውን ስጦታ እንደ ክብሩ መጠን መያዝ እንዲገባን ማስታወስ ያስፈልጋል፡፡ የተሰጠን መዳን የተከፈለውስ የዋጋው ተመን ምን ያህል ነው? ስንል መጠየቅም ተገቢ ነው፡፡ በእርግጥ መዳን ሰዋዊ የዋጋ ተመን ከቶ የለውም፣ ስለዚህ ልኬት አይወጣለትም፣ ተመንም አይተመንለትም፤ የሰው ክፍያ ሊመጥነው ሆነ ደረጃ ሊሰጠው አይችልም፡፡ ሰው ግን ያን ያገኘውን ታላቅ ነገር እጅግ ተጠንቅቆና አክብሮ በእውቀት …
Continue reading እንደተከፈለልህ ተመላለስ (2..)