የእግዚአብሄር መገለጥ፦ምንና ለምን(2…)

ካለፈው የቀጠለ… – እንዲሁ እናንተ ደግሞ የተገለጠውን ቃል በአንደበት ባትናገሩ… ይላል (1ቆሮ.14:9) በፍቅሩ ምክኒያት የተቀበልነውን ደህንነት በፍቅርና በሸክም ድህንነት ለተገባችው የሰው ልጆች ሁሉ ማሳለፍ ምህረት ካገኘ ወገን ይጠበቃል። ስለመዳን እያወሩ አዳኙን ያለመንገር አይቻልም፣ የተሰጣቸውን እያስተዋወቁና በሰፊው እየተናገሩ ሰጪውን ያለማስተዋወቅ ንፉግነት ነው። አይሁድ የአለም ሁሉ አዳኝ ጌታን ሊቀበሉ እጅግ አንገራግረዋል፤ ምህረትና ፈውሱን ከተቀበሉም በሁዋላ የተሸሸጉ አልጠፉም፤ …
Continue reading የእግዚአብሄር መገለጥ፦ምንና ለምን(2…)

የእግዚአብሄር መገለጥ፦ምንና ለምን(1…)

አምላካዊ ምክኒያት አለ? እግዚአብሄር አምላክ በየዘመኑ ላለ ህዝብ እንደ የትውልዱ ቀርቦ ይመጣና የሰውን ልጅ ወደ ራሱ ይጣራል፤ ለጠራው ሰው የጠራበትን ምክኒያት ከማመልከቱ በፊትም የራሱን ማንነት በፊቱ ያውጃል፤ ይህንም በዋናነት አብረሃምና ዘሩ እስራኤልን በጠራው ጊዜ አድርጎአል፡፡ ለእስራኤል አስርቱን ትእዛዝ በሰጠበት ወቅት ራሱን ከማስተዋወቁ ባሻገር ከኔ በቀር ሌላ አምላክ አይሁንላችሁ ሲል አስጠንቅቆ ነበር፡፡ ይህ የጸና አዋጅ በህዝቡ …
Continue reading የእግዚአብሄር መገለጥ፦ምንና ለምን(1…)

ከሰማይ እውቀት መጉደል[3…]

የሰማይ እውቀት የሰማይ የሆነው፣ የመለኮት የሆነው፣ መንፈሳዊ የሆነው ሲሆን ከምድራዊ እውቀት፣ ምጥቀት፣ ፍልስፍናም ይባል ጥልቅ የአጋንንት እውቀት፣ ከነዚህ በላይ የሚልቅ፣ የተለየ፣ የተቀደሰ፣ ሃይል ያለውና አሸናፊ እውቀት የሆነ እርሱ የሰማይ እውቀት ስለሆነ ለእግዚአብሄር መንግስት ማብቃት የሚችልና ከእግዚአብሄር ምንጭ የሚቀዳ መሆኑ የታመነ ነው። የሰማይ እውቀት በመሰረታዊነት በቃሉ ይገለጻል፦ ዳን.10:9-11 ”የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉንም ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ …
Continue reading ከሰማይ እውቀት መጉደል[3…]

ከሰማይ እውቀት መጉደል[2…]

በእግዚአብሄር ከፍ ላለ ህይወት ተጠርተው ያሉ ወገኖች የእግዚአብሄርን ፈቃድ ባለማስተዋልና ባለመከተላቸው ምክኒያት የሰማይ እውቀት ጎደሎ ሲሆንባቸው ኖሮአል። ወደ እግዚአብሄር የተጠጋ የእግዚአብሄርን መንገድ ግን ልብ የማይል ሁሉ ከእውቀት በመጉደሉ በብዙ ይጎዳል። አንድ የእስራኤል መምህር የሆነ ቆርኖሌዎስ የተባለ ሰው በጌታ ፊት ቀርቦ ሲነጋገር ያን ችግር አጉልቶ ሲያሳይ ነበር፡፡ ይህ ሰው በአዋቂዎች ቦታ የተቀመጠ ሌሎችንም በእግዚአብሄር ቃል የሚመራ …
Continue reading ከሰማይ እውቀት መጉደል[2…]

የፍቅር ግዛቶች [7..]

ፍቅር ጥልቅና ሰፊ መለኮታዊ ባህሪ ያለው ነገር ነው። ሰው ስለፍቅር ያለው ግንዛቤና ትርጉዋሜ በእርግጥ ወደ ስጋዊነት የሚያጋድልና ይበልጥ ሰዋዊ ነው። ወደ ስጋዊነት የሚያደላ እንደመሆኑ በአብዛኛው መገለጫው የሚሆነው ስሜት ሲሆን ሰዋዊ እንደመሆኑ የፍቅር ግንኙነቱ የሚያጋድለው በሰውና በሰው መሀከል ነው ማለት ነው። እርግጥ ነው ፍቅር በሰው መሃል ይኖር ዘንድ የፈቀደው የፈጠረን አምላክ ነው። ነገር ግን በሰው መሃል …
Continue reading የፍቅር ግዛቶች [7..]

የፍቅር ግዛቶች [6..]

ስለእግዚአብሄር ማንነት በሚወራበት ስፍራ ሁሉ ከእርሱ ጋር ስለፍቅር ሳይነሳ መታለፍ አይችልም፤ ፍቅር የእግዚአብሄር ታላቅ ባህሪ በመሆኑ በተለይ ለእኛ የእግዚአብሄር ፍቅር ማለት እጅግ ብዙ ትርጉም አለውና እርሱን አንስተን ብናወራ፣ ደጋግመን እግዚአብሄር ስለእኛ የገለጠውን የፍቅር ብርታት ብናስታውስ ሲያንስ እንጂ አይበዛም፡፡ መጽሀፍ ቅዱስ እግዚአብሄር ፍቅር እንደሆነ ያመለክታል፡፡ ፍቅር እንደመሆኑ ሁሉ ይመኩበታል፣  ሁሉ ይጠጉታል፣ ሁሉም ያምኑበታል፡፡ ፍቅሩ ረቂቅና ጥልቅ …
Continue reading የፍቅር ግዛቶች [6..]

በሰንበት ቀን የምስጋና መዝሙር

የአምላክ ምስጋና ሊያውም በሰንበት ቀን (በእግዚአብሄር እረፍት ውስጥ) የሚቀርብ እጅግ የላቀ ደስታና ምህረት የሚያመጣ በመሆኑ ዘማሪው ንጉስ ያን አስተውሎ በመዝሙሩ ጅማሬ በሰንበት ቀን የምስጋና መዝሙር ይላል፡፡ ሲቀጥልም፡- ”እግዚአብሔር ነገሠ፥ ክብርንም ለበሰ፤ እግዚአብሔር ኃይልን ለበሰ፥ ታጠቀም፤ ዓለምን እንዳትናወጥ አጸናት። ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የተዘጋጀ ነው፥ አንተም ከዘላለም ነህ። አቤቱ፥ ወንዞች ከፍ ከፍ አደረጉ፥ ወንዞች ቃሎቻቸውን ከፍ ከፍ …
Continue reading በሰንበት ቀን የምስጋና መዝሙር

የታላቁ አምላክ ሀይል(3..)

ወንጌል በሀይል የሚሰበክ የምስራች ቃል ነው፡፡ ወንጌል በውስጡ ሀይል አለበት፣ የእግዚአብሄር ፈቃድ በውስጡ ስላለና እግዚአብሄር የሚሰራበት የመስቀሉ ቃል መገለጫ በመሆኑ፡፡ ወንጌል የጌታን የደህንነት ስራ የሚገልጥ አዋጅ ነው፤ ስለሆነም እግዚአብሄር አለም ሳይፈጠር ቅዱስ ሊሆኑ በተጠሩ ህይወቶች ውስጥ ሊፈጥር ያቀደውን ጽድቅ በክርስቶስ ኢየሱስ መከራ፣ ሞትና ትንሳኤ በኩል እንደፈጸመው ከፍ አድርጎ የሚያውጅ ቃል ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስ ለሰዎች ሊሰጥ …
Continue reading የታላቁ አምላክ ሀይል(3..)

የታላቁ አምላክ ሀይል(2..)

እግዚአብሄርንና ሀይሉን የሚያውቁ ሰዎች በሁኔታዎች አካሄድና በነገሮች መፈጠር አይደናገጡም፣ በአጋጣሚዎች ድንገት መከሰት አይርበተበቱም፤ ምክኒያቱም ከእነርሱ በላይ ያለውን ስለሚያወቁ፣ ከርሱ በቀር ማንም እንደሌለ ስለሚረዱ፣ ያለ እርሱ ፈቃድ የሚሆን ነገር እንደሌለ ስለሚያውቁ፣ ደግሞም የእርሱ አሳብ ለሰው ልጆች ሁሉ መልካም መሆኑን ስለሚያስተውሉ ነው፡፡ ነቢዩ ኤልሳ በአስጨናቂ ጠላቶች ተከቦ ሳለ የተናገረውን እንመልከት፡- 2ነገ.6:15-17 ”የእግዚአብሔር ሰው ሎሌ ማለዳ ተነሥቶ በወጣ …
Continue reading የታላቁ አምላክ ሀይል(2..)

የታላቁ አምላክ ሀይል(1..)

የእግዚአብሄር ሀይል ወይም መለኮታዊ ሀይል ከእግዚአብሄር ባህሪያት መሀል አንደኛው ነው፡፡ እግዚአብሄር አምላክ ነው፣ ጌታ ነው፣ መድሀኒት ነው፣ ሁሉን የሚችል፣ ሁሉን የሚገዛ፣ በሁሉ የሚኖር፣ ሁሉን በራሱ፣ ለራሱና ከራሱ ያደረገ ድንቅ አምላክ ነው፡፡ ይህ አምላክ ሁሉን በሀይሉ ያደርጋል፡፡ ሀይሉ ጉልበቱን የማንቀሳቀሻ ብርታቱ ነው፡፡ ዘዳ.10:16፤17”እንግዲህ አምላካችሁ እግዚአብሔር የአማልክት አምላክ የጌቶችም ጌታ፥ ታላቅ አምላክ ኃያልም የሚያስፈራም፥ በፍርድ የማያደላ፥ መማለጃም …
Continue reading የታላቁ አምላክ ሀይል(1..)